ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሚክያስ 2:2-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. ዕርሻ ይመኛሉ፤ ይይዙታልም፤ቤት ይመኛሉ፤ ይወስዱታልም፤የሰውን ቤት፣የባልንጀራን ርስት አታልለው ይወስዳሉ።

3. ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ በዚያ ሕዝብ ላይ ጥፋት ላመጣ ዐቅጃለሁ፤ከዚህም ለማምለጥ አትችሉም።ከእንግዲህ በትዕቢት አትመላለሱም፤የመከራ ጊዜ ይሆናልና።

4. በዚያ ቀን ሰዎች ይሣለቁባችኋል፤በሐዘን እንጒርጒሮ እንዲህ እያሉ ያፌዙባችኋል፤‘እኛ ፈጽሞ ጠፍተናል፤የወገኔ ርስት ተከፋፍሎአል።ከእኔ ነጥቆ ወስዶ፣ዕርሻዎቻችንን ላሸነፉን አከፋፈለ።’

5. ስለዚህ በእግዚአብሔር ጉባኤ ውስጥ፣መሬት በዕጣ የሚያካፍል ማንም አይኖርም።

6. ነቢያቶቻቸው፣ “ትንቢት አትናገርብን፤ስለ እነዚህ ነገሮች ትንቢት አትናገር፤ውርደት አይደርስብንም” ይላሉ።

7. የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ እንዲህ ሊባል ይገባልን?“የእግዚአብሔር መንፈስ የማይታገሥ ነውን?እንዲህ ያሉት ነገሮችንስ ያደርጋልን?”“መንገዱ ቀና ለሆነ፣ቃሌ መልካም አያደርግምን?

8. በመጨረሻ በሕዝቤ ላይ ጠላት ሆናችሁተነሣችሁ፤የጦርነት ሐሳብ ሳይኖራቸው፣በሰላም ከሚያልፉ ሰዎች ላይ፣ማለፊያ መጐናጸፊያ ገፈፋችሁ።

9. ከሚወዱት ቤታቸው፣የሕዝቤን ሴቶች አስወጣችኋቸው፤ክብሬን ከልጆቻቸው፣ለዘላለም ወሰዳችሁ።

10. ተነሡና፤ ከዚያ ሂዱ፤ይህ ማረፊያ ቦታችሁ አይደለምና፤ምክንያቱም ረክሶአል፤ክፉኛም ተበላሽቶአል።

11. ሐሰተኛና አታላይ ሰው መጥቶ፣‘ስለ ብዙ የወይን ጠጅና ስለሚያሰክር መጠጥ ትንቢት እነግራችኋለሁ’ ቢል፣ለዚህ ሕዝብ ተቀባይነት ያለው ነቢይ ይሆናል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሚክያስ 2