ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሚክያስ 1:1-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. በይሁዳ ነገሥታት በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን ወደ ሞሬታዊው ወደ ሚክያስ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል፣ ስለ ሰማርያና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ራእይ ይህ ነው፤

2. እናንተ አሕዛብ ሆይ፤ ሁላችሁም ስሙ፤ምድር ሆይ፤ በውስጧም የምትኖሩ ሁሉ አድምጡ፤ጌታ ከቅዱስ መቅደሱ፣ልዑል እግዚአብሔር በእናንተ ላይ ይመሰክርባችኋል።

3. እነሆ፤ እግዚአብሔር ከመኖሪያ ስፍራው ይመጣል፤ወርዶም በምድር ከፍታዎች ላይ ይራመዳል።

4. ተራሮች ከሥሩ ይቀልጣሉ፤ሸለቆዎችም ይሰነጠቃሉ፤በእሳት ፊት እንዳለ ሰም፣በገደል ላይ እንደሚወርድ ፈሳሽ ይሆናሉ።

5. ይህ ሁሉ የሚሆነው ስለ ያዕቆብ በደል፣ስለ እስራኤልም ቤት ኀጢአት ነው።የያዕቆብ በደል ምንድን ነው?ሰማርያ አይደለችምን?የይሁዳስ የኰረብታ መስገጃ ምንድን ነው?ኢየሩሳሌም አይደለችምን?

6. “ስለዚህ ሰማርያን የፍርስራሽ ክምር፣ወይን የሚተከልባትም ስፍራ አደርጋታለሁ፤ድንጋዮቿን ወደ ሸለቆ አወርዳለሁ፤መሠረቷንም ባዶ አደርጋለሁ።

7. ጣዖቶችዋ ሁሉ ይሰባበራሉ፤ለቤተ መቅደሷ የቀረበው ገጸ በረከት በእሳት ይቃጠላል፤ምስሎችዋን ሁሉ እደመስሳለሁ፤ገጸ በረከቷን በዝሙት አዳሪነት እንደ ሰበሰበች ሁሉ፣አሁንም ገጸ በረከትዋ የዝሙት አዳሪነት ዋጋ መቀበያ ይሆናል።

8. በዚህ ምክንያት አለቅሳለሁ፤ ዋይ ዋይም እላለሁ፤ባዶ እግሬንና ዕርቃኔን እሄዳለሁ፤እንደ ቀበሮ አላዝናለሁ፤እንደ ጒጒትም አቃስታለሁ።

9. ቊስሏ የማይሽር ነውና፤ለይሁዳ ተርፎአል፤እስከ ሕዝቤ መግቢያ በር፣እስከ ኢየሩሳሌም እንኳ ደርሶአል።

10. በጌት አታውሩት፤ከቶም አታልቅሱ፤በቤትዓፍራ፣በትቢያ ላይ ተንከባለሉ።

11. እናንት በሻፊር የምትኖሩ፣ዕርቃናችሁን ሆናችሁ በኀፍረት ዕለፉ፤በጸዓናን የሚኖሩከዚያ አይወጡም፤ቤትዔጼል በሐዘን ላይ ናት፤ለእናንተም መጠጊያ ልትሆን አትችልም።

12. ከመከራው መገላገልን በመሻት፣በማሮት የሚኖሩ በሥቃይይወራጫሉ፤እስከ ኢየሩሳሌም በር ሳይቀር፣ክፉ ነገር ከእግዚአብሔር ዘንድ መጥቶአልና።

13. እናንት በለኪሶ የምትኖሩ፣ፈረሶችን ከሠረገላው ጋር አያይዙ፤ለጽዮን ሴት ልጅ፣የኀጢአት መጀመሪያ እናንት ነበራችሁ፤የእስራኤል በደልበእናንተ ዘንድ ተገኝቶአልና።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሚክያስ 1