ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 94:3-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

3. ክፉዎች እስከ መቼ እግዚአብሔር ሆይ፤ ክፉዎች እስከ መቼ ይፈነጫሉ?

4. የእብሪት ቃላት ያዥጐደጒዳሉ፤ክፉ አድራጊዎች ሁሉ ጒራ ይነዛሉ።

5. እግዚአብሔር ሆይ፤ ሕዝብህን አደቀቁ፤ርስትህንም አስጨነቁ።

6. መበለቲቱንና መጻተኛውን ገደሉ፤የድኻ አደጉንም ነፍስ አጠፉ።

7. እነርሱም “እግዚአብሔር አያይም፤የያዕቆብም አምላክ አያስተውልም” አሉ።

8. እናንት በሕዝቡ መካከል ያላችሁ ደነዞች፤ ልብ በሉ፤እናንት ቂሎች፤ ጥበበኞች የምትሆኑት መቼ ነው?

9. ጆሮን የተከለው እርሱ አይሰማምን? ዐይንንስ የሠራ እርሱ አያይምን?

10. ሕዝቦችን በተግሣጽ ወደ መንገድ የሚመልስ፣ዕውቀትንስ ለሰው ልጆች የሚያስተምር አይቀጣምን?

11. እግዚአብሔር የሰው ሐሳብ መና፣ከንቱም እንደሆነ ያውቃል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 94