ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 91:8-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. በዐይንህ ብቻ ትመለከታለህ፤የክፉዎችንም መቀጣት ታያለህ።

9. እግዚአብሔርን መሸሸጊያ፣ልዑልንም መጠጊያህ አድርገኸዋልና።

10. ክፉ ነገር አያገኝህም፤መቅሠፍትም ወደ ድንኳንህ አይገባም፤

11. በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ፣መላእክቱን ስለ አንተ ያዛቸዋልና።

12. እግርህ ከድንጋይ ጋር እንዳይጋጭ፣በእጆቻቸው ወደ ላይ ያነሡሃል።

13. በአንበሳና በእፉኝት ላይ ትጫማለህ፤ደቦሉን አንበሳና ዘንዶውን ትረግጣለህ።

14. “ወዶኛልና እታደገዋለሁ፤ስሜን አውቆአልና እከልለዋለሁ።

15. ይጠራኛል፤ እመልስለታለሁ፤በመከራው ጊዜ ከእርሱ ጋር እሆናለሁ፤አድነዋለሁ፤ አከብረዋለሁ።

16. ረጅም ዕድሜን አጠግበዋለሁ፤ማዳኔንም አሳየዋለሁ።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 91