ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 89:39-50 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

39. ከባሪያህ ጋር የገባኸውን ኪዳን አፈረስህ፤የክብር ዘውዱን ትቢያ ላይ ጥለህ አቃለልኸው።

40. ቅጥሩን ሁሉ አፈራረስህ፤ምሽጉንም ደመሰስህ።

41. ዐላፊ አግዳሚው ሁሉ ዘረፈው፤ለጎረቤቶቹ መዘባበቻ ሆነ።

42. የጠላቶቹን ቀኝ እጅ ከፍ ከፍ አደረግህ፤ባላንጣዎቹም ሁሉ ደስ አላቸው።

43. የሰይፉን ስለት አጠፍህ፤በጦርነትም ጊዜ አልረዳኸውም።

44. ግርማዊነቱን አጠፋህበት፤ዙፋኑንም ከዐፈር ደባለቅኸው።

45. የወጣትነት ዘመኑን አሳጠርኸው፤ዕፍረትንም አከናነብኸው። ሴላ

46. እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህ እስከ መቼ ይሆናል? ራስህንስ ለዘላለም ትሰውራለህን?ቍጣህስ እንደ እሳት የሚነደው እስከ መቼ ነው?

47. ዘመኔ ምን ያህል አጭር እንደሆነች አስብ፤የሰውን ልጆች እንዲያው ለከንቱ ፈጠርሃቸው!

48. ሞትን ሳያይ ሕያው ሆኖ የሚቀርሰው አለን?ራሱን ከሲኦል እጅ ማዳን የሚችል ማን ነው? ሴላ

49. ጌታ ሆይ፤ ለዳዊት በታማኝነትህ የማልህለት፣የቀድሞው ምሕረትህ የት አለ?

50. ጌታ ሆይ፤ ባሪያህ እንዴት እንደ ተፌዘበት፣የብዙ ሰዎችንም ነቀፋ እንደ ታቀፍሁ አስብ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 89