ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 89:13-24 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

13. አንተ ክንደ ብርቱ ነህ፤እጅህ ኀያል ናት፤ ቀኝ እጅህም ከፍ ከፍ ያለች ናት።

14. ጽድቅና ፍትሕ የዙፋንህ መሠረቶች ናቸው፤ምሕረትና ታማኝነት በፊትህ ይሄዳሉ።

15. እግዚአብሔር ሆይ፤ እልልታን የሚያውቅ፣በፊትህም ብርሃን የሚሄድ ሕዝብ ምስጉን ነው።

16. ቀኑን ሙሉ በስምህ ደስ ይላቸዋል፤በጽድቅህም ሐሤት ያደርጋሉ፤

17. አንተ የብርታታቸው ክብር ነህና፤በሞገስህም ቀንዳችንን ከፍ ከፍ አደረግህ።

18. ጋሻችን የእግዚአብሔር ነውና፤ንጉሣችንም የራሱ የእስራኤል ቅዱስ ነው።

19. በዚያን ጊዜ በራእይ ተናገርህ፤ታማኝ ሕዝብህንም እንዲህ አልህ፤“ኀያሉን ሰው ሥልጣን አጐናጸፍሁት፤ከሕዝብ መካከል የተመረጠውንም ከፍ ከፍ አደረግሁት።

20. ባሪያዬን ዳዊትን አገኘሁት፤በተቀደሰው ዘይቴም ቀባሁት።

21. እጄ ይደግፈዋል፤ክንዴም ያበረታዋል።

22. በጠላት አይበለጥም፤ክፉ ሰውም አይበግረውም።

23. ባላንጣዎቹን በፊቱ አደቅቃቸዋለሁ፤ጠላቶቹንም እቀጠቅጣለሁ።

24. ታማኝነቴና ምሕረቴ ከእርሱጋር ይሆናል፤በስሜም ቀንዱ ከፍ ከፍ ይላል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 89