ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 89:1-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ስለ እግዚአብሔር ምሕረት ለዘለላለም እዘምራለሁ፤በአፌም ታማኝነትህን ከትውልድ እስከ ትውልድ እገልጻለሁ።

2. ምሕረትህን ለዘላለም እንደምትመሠርት፣ታማኝነትህንም በሰማይ እንደምታጸና እናገራለሁና።

3. አንተም እንዲህ ብለሃል፤ “ከመረጥሁት ጋር ኪዳን ገብቻለሁ፤ለባሪያዬ ለዳዊት ምያለሁ፤

4. ‘ዘርህን ለዘላለም እተክላለሁ፤ዙፋንህንም ከትውልድ እስከ ትውልድ አጸናለሁ።’ ” ሴላ

5. እግዚአብሔር ሆይ፤ ሰማያት ድንቅ ሥራህን፣ታማኝነትህንም በቅዱሳን ጉባኤ መካከል ያወድሳሉ፤

6. በላይ በሰማያት ከእግዚአብሔር ጋር ማን ሊስተካከል ይችላል?ከሰማያውያን ፍጥረታትስ መካከል ማን እግዚአብሔርን ይመስለዋል?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 89