ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 86:6-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. እግዚአብሔር ሆይ፤ ጸሎቴን አድምጥ፤የልመናዬን ጩኸት ስማ።

7. አንተ ስለምትመልስልኝ፣በመከራዬ ቀን ወደ አንተ እጣራለሁ።

8. ጌታ ሆይ፤ ከአማልክት መካከል እንደ አንተ ያለ የለም፤ከአንተም ሥራ ጋር የሚወዳደር ሥራ የለም።

9. ጌታ ሆይ፤ አንተ የሠራሃቸው ሕዝቦች ሁሉ፣መጥተው በፊትህ ይሰግዳሉ፤ለስምህም ክብር ይሰጣሉ፤

10. አንተ ታላቅ ነህና፤ ታምራትም ትሠራለህ፤አንተ ብቻህን አምላክ ነህ።

11. እግዚአብሔር ሆይ፤ መንገድህን አስተምረኝ፤በእውነትህም እሄዳለሁ፤ስምህን እፈራ ዘንድ፣ያልተከፋፈለ ልብ ስጠኝ።

12. ጌታ አምላኬ ሆይ፤ በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፤ስምህንም ለዘላለም አከብራለሁ፤

13. ለእኔ ያሳየሃት ምሕረት ታላቅ ናትና፤ነፍሴንም ከሲኦል ጥልቀት አውጥተሃል።

14. አምላክ ሆይ፤ እብሪተኞች ተነሥተውብኛል፤የዐመፀኞችም ጉባኤ ነፍሴን ይሿታል፤አንተንም ከምንም አልቈጠሩም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 86