ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 83:1-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. አምላክ ሆይ፤ ዝም አትበል፤አምላክ ሆይ፤ ጸጥ አትበል፤ ጭጭ አትበል።

2. ጠላቶችህ እንዴት እንደ ተነሣሡ፣ባላንጣዎችህም እንዴት ራሳቸውን ቀና ቀና እንዳደረጉ ተመልከት።

3. በሕዝብህ ላይ በተንኰል አሤሩ፤በውድ ልጆችህ ላይ በአንድነት ተመካከሩ።

4. “የእስራኤል ስም ከእንግዲህ እንዳይታወስ፣ኑና ሕዝብ እንዳይሆኑ እንደምስሳቸው” አሉ።

5. በአንድ ሐሳብ ተስማምተው ተማከሩ፤በአንተም ላይ ተማማሉ፤

6. የኤዶምና የእስማኤላውያን ድንኳኖች፣የሞዓብና የአጋራውያን ድንኳኖች፣

7. ጌባል፣ አሞንና አማሌቅ፣ፍልስጥኤምም ከጢሮስ ሕዝብ ጋር ሆነው ዶለቱ፤

8. አሦርም ከእነርሱ ጋር ተባበረ፤የሎጥ ልጆችም ረዳት ሆነ። ሴላ

9. በምድያም ላይ እንዳደረግኸው አድርግባቸው፤በቂሶንም ወንዝ በሲሣራና በኢያቢስ ላይ ያደረስኸው ይድረስባቸው።

10. እነርሱም በዐይንዶር ጠፉ፤እንደ ምድርም ጒድፍ ሆኑ።

11. መኳንንታቸውን እንደ ሔሬብና እንደ ዜብ፣መሳፍንታቸውንም ሁሉ እንደ ዛብሄልና እንደ ስልማና አድርጋቸው፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 83