ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 82:1-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር በአማልክት ጉባኤ መካከል ተሰየመ፤በአማልክትም ላይ ይፈርዳል፤ እንዲህም ይላል፦

2. “ፍትሕን የምታጓድሉት እስከ መቼ ነው?ለክፉዎች የምታደሉትስ እስከ መቼ ነው? ሴላ

3. ለዐቅመ ቢሶችና ለድኻ አደጎች ፍረዱላቸው፤የችግረኛውንና የምስኪኑን መብት አስከብሩ።

4. ወገን የሌለውንና ችግረኛውን ታደጉ፤ከግፈኛውም እጅ አስጥሏቸው።

5. “ዕውቀትም ማስተዋልም የላቸውም፤በጨለማ ውስጥ ወዲያ ወዲህ ይመላለሳሉ፤የምድርም መሠረቶች ሁሉ ተናወጡ።

6. “እኔም፤ ‘እናንተ አማልክት ናችሁ፤ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ’ አልሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 82