ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 81:6-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. “ትከሻውን ከሸክም ገላገልሁት፤እጁንም ቅርጫት ከመያዝ አሳረፍሁ።

7. በመከራህ ጊዜ ጠራኸኝ፤ እኔም ታደግሁህ፤በነጐድጓድ መሰወሪያ ውስጥ መለስሁልህ፤በመሪባ ውሃ ዘንድ ፈተንሁህ። ሴላ

8. “ሕዝቤ ሆይ፤ ሳስጠነቅቅህ ስማኝ፤እስራኤል ሆይ፤ ምነው ብታደምጠኝ!

9. በአንተ ዘንድ ባዕድ አምላክ አይኑር፤ለሌላም አምላክ አትስገድ።

10. ከግብፅ ምድር ያወጣሁህ፣እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ነኝ፤አፍህን በሰፊው ክፈተው፤ እኔም እሞላዋለሁ።

11. “ሕዝቤ ግን አላደመጠኝም፤እስራኤልም እጅ አልሰጥ አለኝ።

12. ስለዚህ በገዛ ዕቅዳቸው እንዲሄዱ፣አሳልፌ ለደንዳናው ልባቸው ሰጠኋቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 81