ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 80:4-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤በሕዝብህ ጸሎት ላይ ቍጣህ የሚነደው፣እስከ መቼ ድረስ ነው?

5. የእንባ እንጀራ አበላሃቸው፤ስፍር የሞላ እንባም አጠጣሃቸው።

6. ለጎረቤቶቻችን የጠብ ምክንያት አደረግኸን፤ጠላቶቻችንም ተሣሣቁብን።

7. የሰራዊት አምላክ ሆይ፤ መልሰን፤እንድንም ዘንድ፣ፊትህን አብራልን።

8. ከግብፅ የወይን ግንድ አመጣህ፤አሕዛብን አባርረህ እርሷን ተከልሃት።

9. መሬቱን መነጠርህላት፤እርሷም ሥር ሰዳ አገሩን ሞላች።

10. ተራሮች በጥላዋ ተሸፈኑ፤ግዙፍ ዝግቦችም በቅርንጫፎቿ ተጠለሉ።

11. ቅርንጫፎቿን እስከ ባሕሩ፣ቊጥቋጦዋንም እስከ ወንዙ ዘረጋች።

12. ታዲያ ዐላፊ አግዳሚው ፍሬዋን እንዲለቅም፣ለምን ቅጥሯን አፈረስህ?

13. ዕርያ ከዱር ወጥቶ ያበለሻሻታል፤በሜዳ የሚንጋጋ እንስሳ ሁሉ ይበላታል።

14. የሰራዊት አምላክ ሆይ፤ እንግዲህ ወደ እኛ ተመለስ፤ከሰማይ ተመልከት፤ እይም፤ይህችን የወይን ተክል ተንከባከባት፤

15. ይህች ቀኝ እጅህ የተከላት ቡቃያ፣ለራስህ ያጸደቅሃት ተክል ናት።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 80