4. እኛም ለጎረቤቶቻችን መዘባበቻ፣በዙሪያችንም ላሉት መሣቂያ መሣለቂያ ሆንን።
5. እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህ እስከ መቼ ነው?የምትቈጣውስ ለዘላለም ነውን?ቅናትህስ እንደ እሳት ሲነድ ይኖራልን?
6. በማያውቁህ ሕዝቦች ላይ፣ስምህን በማይጠሩ፣መንግሥታት ላይ፣መዓትህን አፍስስ፤
7. ያዕቆብን በልተውታልና፤መኖሪያ ቦታውንም ባድማ አድርገዋል።
8. የአባቶቻችንን ኀጢአት በእኛ ላይ አትቍጠርብን፤ምሕረትህ ፈጥና ወደ እኛ ትምጣ፤በጭንቅ ላይ እንገኛለንና።
9. አዳኛችን የሆንህ አምላክ ሆይ፤ስለ ስምህ ክብር ብለህ እርዳን፤ስለ ስምህ ስትል፣ታደገን፤ ኀጢአታችንንም ይቅር በል።