ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 78:48-55 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

48. ከብቶቻቸውን ለበረዶ፣የከብት መንጋቸውን ለመብረቅ እሳት ዳረገ።

49. ጽኑ ቍጣውን በላያቸው ሰደደ፤መዓቱን፣ የቅናቱን ቍጣናመቅሠፍቱን ላከባቸው፤አጥፊ የመላእክት ሰራዊትም ሰደደባቸው።

50. ለቊጣው መንገድ አዘጋጀ፤ነፍሳቸውንም ከሞት አላተረፈም፤ነገር ግን ሕይወታቸውን ለመቅሠፍት አሳልፎ ሰጠ።

51. የዐፍላ ጒልበታቸው መጀመሪያ የሆኑትን በካም ድንኳን፣በኵሮቻቸውንም ሁሉ በግብፅ ምድር ፈጀ።

52. ሕዝቡን ግን እንደ በግ አወጣቸው፤በምድረ በዳም እንደ መንጋ መራቸው።

53. በሰላም መራቸው፤ እነርሱም አልፈሩም፤ጠላቶቻቸውን ግን ባሕር ዋጣቸው።

54. ቀኝ እጁም ወዳስገኘችው ወደዚህ ተራራ፣ወደ ቅድስት ምድር አገባቸው።

55. ሕዝቦችን ከፊታቸው አባረረ፤ምድራቸውን ርስት አድርጎ አከፋፈላቸው፤የእስራኤልንም ነገዶች በጠላቶቻቸው ቤት አኖረ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 78