ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 78:41-53 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

41. ደግመው ደጋግመው እግዚአብሔርን ተፈታተኑት፤የእስራኤልንም ቅዱስ አስቈጡት።

42. እነርሱን በዚያን ቀን ከጠላት የታደገበትን፣ያን ኀይሉን አላስታወሱም፤

43. በግብፅ ያደረገውን ታምራዊ ምልክት፣በጣኔዎስም በረሓ ያሳየውን ድንቅ ሥራ አላሰቡም።

44. ወንዞቻቸውን ወደ ደም ለወጠ፤ከጅረቶቻቸውም መጠጣት አልቻሉም።

45. የዝንብ ሰራዊት ሰደደባቸው፤ ነደፏቸውም፤ጓጒንቸርም ላከባቸው፤ ሰዎችንም አጠፉ።

46. አዝመራቸውን ለኵብኵባ፣ሰብላቸውንም ለአንበጣ ሰጠባቸው።

47. የወይን ተክላቸውን በበረዶ፣የበለስ ዛፋቸውንም በውርጭ አጠፋ።

48. ከብቶቻቸውን ለበረዶ፣የከብት መንጋቸውን ለመብረቅ እሳት ዳረገ።

49. ጽኑ ቍጣውን በላያቸው ሰደደ፤መዓቱን፣ የቅናቱን ቍጣናመቅሠፍቱን ላከባቸው፤አጥፊ የመላእክት ሰራዊትም ሰደደባቸው።

50. ለቊጣው መንገድ አዘጋጀ፤ነፍሳቸውንም ከሞት አላተረፈም፤ነገር ግን ሕይወታቸውን ለመቅሠፍት አሳልፎ ሰጠ።

51. የዐፍላ ጒልበታቸው መጀመሪያ የሆኑትን በካም ድንኳን፣በኵሮቻቸውንም ሁሉ በግብፅ ምድር ፈጀ።

52. ሕዝቡን ግን እንደ በግ አወጣቸው፤በምድረ በዳም እንደ መንጋ መራቸው።

53. በሰላም መራቸው፤ እነርሱም አልፈሩም፤ጠላቶቻቸውን ግን ባሕር ዋጣቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 78