ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 78:37-46 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

37. ልባቸው በእርሱ የጸና አልነበረም፤ለኪዳኑም ታማኞች አልነበሩም።

38. እርሱ ግን መሓሪ እንደ መሆኑ፣በደላቸውን ይቅር አለ፤አላጠፋቸውም፤ቊጣውን ብዙ ጊዜ ገታ፤መዓቱንም ሁሉ አላወረደም።

39. ወጥቶ የማይመለስ ነፋስ፣ሥጋ ለባሾች መሆናቸውን አሰበ።

40. በምድረ በዳ ስንት ጊዜ ዐመፁበት!በበረሓስ ምን ያህል አሳዘኑት!

41. ደግመው ደጋግመው እግዚአብሔርን ተፈታተኑት፤የእስራኤልንም ቅዱስ አስቈጡት።

42. እነርሱን በዚያን ቀን ከጠላት የታደገበትን፣ያን ኀይሉን አላስታወሱም፤

43. በግብፅ ያደረገውን ታምራዊ ምልክት፣በጣኔዎስም በረሓ ያሳየውን ድንቅ ሥራ አላሰቡም።

44. ወንዞቻቸውን ወደ ደም ለወጠ፤ከጅረቶቻቸውም መጠጣት አልቻሉም።

45. የዝንብ ሰራዊት ሰደደባቸው፤ ነደፏቸውም፤ጓጒንቸርም ላከባቸው፤ ሰዎችንም አጠፉ።

46. አዝመራቸውን ለኵብኵባ፣ሰብላቸውንም ለአንበጣ ሰጠባቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 78