ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 78:33-37 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

33. ስለዚህ ዘመናቸውን በከንቱ፣ዕድሜአቸውንም በድንጋጤ ጨረሰ።

34. እርሱ በገደላቸው ጊዜ ፈለጉት፤ከልባቸው በመሻትም ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ።

35. እግዚአብሔር ዐለታቸው፣ልዑል አምላክ ቤዛቸው እንደሆነ አሰቡ።

36. ነገር ግን በአፋቸው ሸነገሉት፤በአንደበታቸው ዋሹት።

37. ልባቸው በእርሱ የጸና አልነበረም፤ለኪዳኑም ታማኞች አልነበሩም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 78