ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 78:15-23 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. ዐለቱን በምድረ በዳ ሰነጠቀ፤እንደ ባሕር የበዛ ውሃ አጠጣቸው፤

16. ምንጭ ከቋጥኝ አፈለቀ፤ውሃን እንደ ወንዝ አወረደ።

17. እነርሱ ግን በምድረ በዳ በልዑል ላይ በማመፅ፣በእርሱ ላይ ኀጢአት መሥራታቸውን ቀጠሉ።

18. እጅግ የተመኙትን ምግብ በመጠየቅ፣እግዚአብሔርን በልባቸው ተፈታተኑት።

19. እንዲህም ብለው በእግዚአብሔር ላይ ተናገሩ፤“እግዚአብሔር በምድረ በዳ ማዕድ ማሰናዳት ይችላልን?

20. ዐለቱን ሲመታ፣ ውሃ ተንዶለዶለ፤ጅረቶችም ጐረፉ፤ታዲያ፣ እንጀራንም መስጠት ይችላል?ሥጋንስ ለሕዝቡ ሊያቀርብ ይችላል?”

21. እግዚአብሔር ይህን ሲሰማ፣ እጅግ ተቈጣ፤በያዕቆብም ላይ እሳት ነደደ፤ቍጣውም በእስራኤል ላይ ተነሣ፤

22. በእግዚአብሔር አላመኑምና፤በእርሱም ማዳን አልታመኑም።

23. እርሱ ግን ከላይ ደመናትን አዘዘ፤የሰማይንም ደጆች ከፈተ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 78