ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 78:12-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. አባቶቻቸው በዐይናቸው እያዩ፣በግብፅ አገር፣ በጣኔዎስ ምድር ታምራት አደረገ።

13. ባሕሩን ከፍሎ አሻገራቸው፤ውሃውንም እንደ ክምር አቆመ።

14. ቀን በደመና መራቸው፤ሌሊቱንም ሁሉ በእሳት ብርሃን።

15. ዐለቱን በምድረ በዳ ሰነጠቀ፤እንደ ባሕር የበዛ ውሃ አጠጣቸው፤

16. ምንጭ ከቋጥኝ አፈለቀ፤ውሃን እንደ ወንዝ አወረደ።

17. እነርሱ ግን በምድረ በዳ በልዑል ላይ በማመፅ፣በእርሱ ላይ ኀጢአት መሥራታቸውን ቀጠሉ።

18. እጅግ የተመኙትን ምግብ በመጠየቅ፣እግዚአብሔርን በልባቸው ተፈታተኑት።

19. እንዲህም ብለው በእግዚአብሔር ላይ ተናገሩ፤“እግዚአብሔር በምድረ በዳ ማዕድ ማሰናዳት ይችላልን?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 78