ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 68:2-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. ጢስ እንደሚበንን፣እንዲሁ አብንናቸው።ሰም በእሳት ፊት እንደሚቀልጥ፣ክፉዎችም እንዲሁ ከእግዚአብሔር ፊት ይጥፉ።

3. ጻድቃን ግን ደስ ይበላቸው፤በእግዚአብሔር ፊት ሐሤት ያድርጉ፤ደስታንና ፍስሓን የተሞሉ ይሁኑ።

4. ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ ለስሙም ተቀኙ፤በደመናት ላይ የሚሄደውን ከፍ አድርጉት፤ስሙ እግዚአብሔር በተባለው ፊት፣እጅግ ደስ ይበላችሁ።

5. እግዚአብሔር በተቀደሰ ማደሪያው፣ለድኻ አደጉ አባት፣ ለባልቴቲቱም ተሟጋች ነው።

6. እግዚአብሔር ብቸኞችን በቤተ ሰብ መካከል ያኖራል፤እስረኞችን ነጻ አውጥቶ ያስፈነድቃል፤ዐመፀኞች ግን ምድረ በዳ ይኖራሉ።

7. እግዚአብሔር ሆይ፤ በሕዝብህ ፊት በወጣህ ጊዜ፣በምድረ በዳም በተጓዝህ ጊዜ፣ ሴላ

8. በሲና አምላክ፣ በእግዚአብሔር ፊት፣በእስራኤል አምላክ፣ በእግዚአብሔር ፊት፣ምድር ተንቀጠቀጠች፤ሰማያትም ዶፍ አወረዱ።

9. እግዚአብሔር ሆይ፣ በቂ ዝናብ አዘነብህ፤ክው ብሎ የደረቀውን ርስትህን አረሰረስህ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 68