ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 65:8-13 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. ርቀው በምድር ዳርቻ ያሉት ከድንቅ ሥራህ የተነሣ ይደነግጣሉ፤የንጋትንና የምሽትን መምጫዎች፣በደስታ እልል እንዲሉ ታደርጋቸዋለህ።

9. ምድርን ትጐበኛለህ፤ ታጠጣለህም፤እጅግ ታበለጽጋታለህም።ለሰዎች እህልን ይለግሱ ዘንድ፣የእግዚአብሔር ወንዞች ውሃን የተሞሉ ናቸው፤አንተ እንዲህ እንዲሆን ወስነሃልና።

10. ትልሟን በውሃ ታረሰርሳለህ፤ቦይዋን ታስተካክላለህ፤በካፊያ ታለሰልሳለህ፤ቡቃያዋንም ትባርካለህ።

11. ለዘመኑ በጎነትህን ታጐናጽፈዋለህ፤ሠረገላህም በረከትን ተሞልቶ ይፈስሳል።

12. የምድረ በዳው ሣር እጅግ ለመለመ፤ኰረብቶችም ደስታን ተጐናጸፉ።

13. ሜዳዎች መንጋ በመንጋ ሆኑ፤ሸለቆችም በእህል ተሸፈኑ፤እልል ይላሉ፤ ይዘምራሉም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 65