ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 42:7-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. በፏፏቴህ ማስገምገም፣አንዱ ጥልቅ ሌላውን ጥልቅ ይጣራል፤ማዕበልህና ሞገድህ ሁሉ፣ሙሉ በሙሉ አጥለቀለቀኝ።

8. እግዚአብሔር ምሕረቱን በቀን ያዝዛል፤ዝማሬውም በሌሊት በእኔ ዘንድ አለ፤ይህም ለሕይወቴ አምላክ የማቀርበው ጸሎት ነው።

9. እግዚአብሔር ዐለቴን፣“ለምን ረሳኸኝ?ጠላትስ እያስጨነቀኝ፣ለምን በሐዘን እመላለሳለሁ?” እለዋለሁ።

10. ጠላቶቼ ቀኑን ሙሉ፣“አምላክህ የት አለ?” እያሉ፣በነገር ጠዘጠዙኝ፣ዐጥንቴም ደቀቀ።

11. ነፍሴ ሆይ፤ ለምን ትተክዢያለሽ?ለምንስ በውስጤ ትታወኪያለሽ?ተስፋሽን በአምላክ ላይ አድርጊ፣አዳኜና አምላኬን፣ገና አመሰግነዋለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 42