ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 35:7-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. ያለ ምክንያት ወጥመዳቸውን በስውር አስቀምጠውብኛልና፤ያለ ምክንያት ለነፍሴ ጒድጓድ ቈፍረውላታል።

8. ያልታሰበ ጥፋት ይምጣባቸው፤የሰወሩት ወጥመድ ይያዛቸው፤ይጠፉም ዘንድ ወደ ጒድጓዱ ይውደቁ።

9. ነፍሴም በእግዚአብሔር ደስ ይላታል፤በማዳኑም ሐሤት ታደርጋለች።

10. የሠራ አካላቴ እንዲህ ይልሃል፤“እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ አንተ ማን አለ?ድኻውን ከእርሱ ከሚበረቱ፣ችግረኛውንና ምስኪኑን ከቀማኞች ታድናለህ”።

11. ጨካኝ ምስክሮች ተነሡ፤ስለማላውቀውም ነገር ጠየቁኝ።

12. በበጎ ፈንታ ክፉ መለሱልኝ፤ነፍሴንም ብቸኛ አደረጓት።

13. እኔ ግን እነርሱ በታመሙ ጊዜ ማቅ ለበስሁ፤ነፍሴንም በጾም አደከምኋት፤ጸሎቴም መልስ አጥቶ ወደ ጒያዬ ተመለሰ።

14. ለወዳጄ ወይም ለወንድሜ እንደማደርግ፣እየተንቈራጠጥሁ አለቀስሁ፤ለእናቴም እንደማለቅስ፣በሐዘን ዐንገቴን ደፋሁ።

15. እነርሱ ግን እኔ ስሰናከል በእልልታ ተሰበሰቡ፤ግፈኞች በድንገት ተሰበሰቡብኝ፤ያለ ዕረፍትም ቦጫጨቁኝ።

16. እንደ ምናምንቴዎች አፌዙብኝ፤ጥርሳቸውንም አፋጩብኝ።

17. ጌታ ሆይ፤ እስከ መቼ ዝም ብለህ ታያለህ?ነፍሴን ከክፉ ሥራቸው፣ብርቅ ሕይወቴን ከአንበሶች ታደጋት።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 35