ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 35:15-24 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. እነርሱ ግን እኔ ስሰናከል በእልልታ ተሰበሰቡ፤ግፈኞች በድንገት ተሰበሰቡብኝ፤ያለ ዕረፍትም ቦጫጨቁኝ።

16. እንደ ምናምንቴዎች አፌዙብኝ፤ጥርሳቸውንም አፋጩብኝ።

17. ጌታ ሆይ፤ እስከ መቼ ዝም ብለህ ታያለህ?ነፍሴን ከክፉ ሥራቸው፣ብርቅ ሕይወቴን ከአንበሶች ታደጋት።

18. በታላቅ ጉባኤ መካከል አመሰግንሃለሁ፤ብዙ ሕዝብ በተሰበሰበበትም አወድስሃለሁ።

19. ከምድር ተነሥተው ጠላቶቼ የሆኑት፣በላዬ ደስ አይበላቸው፤እንዲያው የሚጠሉኝ፣በዐይናቸው አይጣቀሱብኝ።

20. የሰላም ንግግር ከአፋቸው አይወጣም፤ዳሩ ግን በምድሪቱ በጸጥታ በሚኖሩት ላይ፣ነገር ይሸርባሉ።

21. አፋቸውን አስፍተው ከፈቱብኝ፤“ዕሠይ! ዕሠይ! በዐይናችን አየነው” አሉ።

22. እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህን አይተሃልና ዝም አትበል፤ጌታ ሆይ፤ ከእኔ አትራቅ።

23. አምላኬ፣ ጌታዬ፤ ለእኔ ለመሟገት ተነሥ!ልትከራከርልኝም ተንቀሳቀስ።

24. እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ በጽድቅህ ፍረድልኝ፤በእኔም ላይ ደስ አይበላቸው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 35