ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 33:6-20 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. በእግዚአብሔር ቃል ሰማያት ተሠሩ፤በአፉም እስትንፋስ የከዋክብት ሰራዊት።

7. የባሕርን ውሃ በአንድ ዕቃ ይሰበስባል፤ቀላዩንም በአንድ ስፍራ ያከማቻል።

8. ምድር ሁሉ እግዚአብሔርን ትፍራው፤በዓለም የሚኖር ሕዝብ ሁሉ በፊቱ ይንቀጥቀጥ።

9. እርሱ ተናግሮአልና ሆኑ፤አዞአልና ጸኑም።

10. እግዚአብሔር የሕዝቦችን ምክክር ከንቱ ያደርጋል፤የሕዝብንም ዕቅድ ያጨናግፋል።

11. የእግዚአብሔር ሐሳብ ግን ለዘላለም ይጸናል፤የልቡም ሐሳብ ለትውልድ ሁሉ ነው።

12. እግዚአብሔር አምላኩ የሆነው ሕዝብ፣ለርስቱ የመረጠውም ወገን የተባረከ ነው።

13. እግዚአብሔር ከሰማይ ይመለከታል፤የሰውንም ልጆች ሁሉ ያያል፤

14. ከማደሪያው ቦታ ሆኖ፣በምድር ወደሚኖሩት ሁሉ ይመለከታል፤

15. እርሱ የሁሉን ልብ የሠራ፣የሚያደርጉትን ሁሉ የሚያስተውል ነው።

16. ንጉሥ በሰራዊቱ ታላቅነት አይድንም፤ጀግናም በኀይሉ ብርታት አያመልጥም።

17. በፈረስ ድል አደርጋለሁ ማለት ከንቱ ተስፋ ነው፤በብርቱ ጒልበቱም ማንንም አያድንም።

18. እነሆ፤ የእግዚአብሔር ዐይኖች በሚፈሩት ላይ ናቸው፤ምሕረቱንም በሚጠባበቁት ላይ አትኵረዋል።

19. በዚህም ነፍሳቸውን ከሞት ያድናል፤በራብ ዘመንም በሕይወት ያኖራቸዋል።

20. ነፍሳችን እግዚአብሔርን ተስፋ ታደርጋለች፤እርሱ ረዳታችንና መጠጊያችን ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 33