ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 32:8-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. አስተምርሃለሁ፤ በምትሄድበትም መንገድ እመራሃለሁ፤እመክርሃለሁ፤ በዐይኔም እከታተልሃለሁ።

9. በልባብና በልጓም ካልተገሩ በቀር፣ወደ አንተ እንደማይቀርቡት፣ማስተዋል እንደሌላቸው፣እንደ ፈረስና እንደ በቅሎ አትሁኑ።

10. የክፉዎች ዋይታ ብዙ ነው፤ በእግዚአብሔር የሚታመን ግን፣ምሕረት ይከበዋል።

11. ጻድቃን ሆይ፤ በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ፤ ሐሤትም አድርጉ፤ቅን ልብ ያላችሁም ሁሉ እልል በሉ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 32