ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 26:1-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እግዚአብሔር ሆይ፤ ያለ ነቀፋ እንደ መሆኔ፣አንተው ፍረድልኝ።ወዲያ ወዲህ ሳልልም፣ በእግዚአብሔር ታምኛለሁ።

2. እግዚአብሔር ሆይ፤ ፈትነኝ፤መርምረኝም፤ልቤንና ውስጤን መርምር፤

3. ምሕረትህ ከፊቴ አልተለየምና፣በእውነትህም ተመላለስሁ።

4. ከማይረቡ ጋር አልተቀመጥሁም፤ከግብዞችም ጋር አልተባበርሁም።

5. የክፉዎችን ማኅበር ተጸየፍሁ፤ከዐመፀኞችም ጋር አልቀመጥም።

6. እጆቼን በየዋህነት እታጠባለሁ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ መሠዊያህንም እዞራለሁ፤

7. የምስጋናን ድምፅ አሰማ ዘንድ፣ታምራትህንም አወራ ዘንድ ነው።

8. እግዚአብሔር ሆይ፤ የምትኖርበትን ቤት፣የክብርህን ማደሪያ ቦታ ወደድሁ።

9. ነፍሴን ከኀጢአተኞች ጋር፣ሕይወቴንም ከደም አፍሳሾች ጋር አታስወግዳት።

10. በእነርሱ እጅ የተንኰል ዕቅድ አለ፤ቀኝ እጃቸውም ጒቦን ያጋብሳል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 26