ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 142:1-4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ድምፄን ከፍ አድርጌ ወደ እግዚአብሔር እጮኻለሁ፤ድምፄን ከፍ አድርጌ ወደ እግዚአብሔር ልመና አቀርባለሁ።

2. ብሶቴን በፊቱ አፈስሳለሁ፤ችግሬንም በፊቱ እናገራለሁ።

3. መንፈሴ በውስጤ ሲዝል፣መንገዴን የምታውቅ አንተ ነህ፤በመተላለፊያ መንገዴ ላይ፤ወጥመድ በስውር ዘርግተውብኛል።

4. ወደ ቀኜ ተመልከት፤ እይም፤ስለ እኔ የሚገደው የለም፤ማምለጫም የለኝም፤ስለ ነፍሴም ደንታ ያለው የለም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 142