ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 119:31-39 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

31. እግዚአብሔር ሆይ፤ ከምስክርነትህ ጋር ተጣብቄአለሁ፤አሳልፈህ ለውርደት አትስጠኝ።

32. ልቤን አስፍተህልኛልና፣በትእዛዛትህ መንገድ እሮጣለሁ።

33. እግዚአብሔር ሆይ፤ የሥርዐትህን መንገድ አስተምረኝ፤እኔም እስከ መጨረሻው እጠብቀዋለሁ።

34. ሕግህን እንድጠብቅ፣ በፍጹም ልቤም እንድታዘዘው፣ ማስተዋልን ስጠኝ።

35. በእርሷ ደስ ይለኛልና፣በትእዛዝህ መንገድ ምራኝ።

36. ከራስ ጥቅም ይልቅ፣ልቤን ወደ ምስክርነትህ አዘንብል።

37. ከንቱ ነገር ከማየት ዐይኖቼን መልስ፤በራስህ መንገድ እንደ ገና ሕያው አድርገኝ።

38. ትፈራ ዘንድ፣ለአገልጋይህ የገባኸውን ቃል ፈጽም።

39. የምፈራውን መዋረድ ከእኔ አርቅ፤ደንብህ መልካም ነውና።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 119