ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 119:124-133 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

124. ለባሪያህ እንደ ምሕረትህ መጠን አድርግ፤ሥርዐትህንም አስተምረኝ።

125. እኔ ባሪያህ ነኝ፤ምስክርነትህን ዐውቅ ዘንድ ማስተዋልን ስጠኝ።

126. እግዚአብሔር ሆይ፤ሕግህ እየተጣሰ ነውና፣ጊዜው አንተ የምትሠራበት ነው።

127. ስለዚህ ከወርቅ፣ ከንጹሕ ወርቅ ይልቅ፣ትእዛዛትህን ወደድሁ።

128. መመሪያህ ሙሉ በሙሉ ልክ ነው አልሁ፤ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ሁሉ ጠላሁ።

129. ምስክርነትህ ሁሉ ድንቅ ነው፤ስለዚህ ነፍሴ ትጠብቀዋለች።

130. የቃልህ ትርጓሜ ያበራል፤አላዋቂዎችንም አስተዋዮች ያደርጋል።

131. ትእዛዝህን ናፍቄአለሁና፣አፌን ከፈትሁ፤ አለከለክሁም።

132. ስምህን ለሚወዱ ማድረግ ልማድህ እንደሆነ ሁሉ፣ወደ እኔ ተመልሰህ፣ ምሕረት አድርግልኝ።

133. አካሄዴን እንደ ቃልህ ቀና አድርግልኝ፤ኀጢአትም በላዬ እንዲሠለጥን አትፍቀድ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 119