ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 115:1-11 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. ለእኛ ሳይሆን፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ ለእኛ ሳይሆን፣ስለ ምሕረትህና ስለ እውነትህ፣ለስምህ ክብርን ስጥ።

2. አሕዛብ፣ “አምላካቸው የት አለ?” ለምን ይበሉ?

3. አምላካችንስ በሰማይ ነው፤እርሱ ደስ የሚለውን ያደርጋል።

4. የእነርሱ ጣዖታት ግን የሰው እጅ የሠራቸው፣ብርና ወርቅ ናቸው።

5. አፍ አላቸው፤ አይናገሩም፤ዐይን አላቸው፤ አያዩም፣

6. ጆሮ አላቸው፤ አይሰሙም፤አፍንጫ አላቸው፤ አያሸቱም፤

7. እጅ አላቸው፤ አይዳስሱም፤እግር አላቸው፤ አይሄዱም፤በጒሮሮአቸውም ድምፅ አይፈጥሩም።

8. እነዚህን የሚያበጁ፣የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ።

9. የእስራኤል ቤት ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

10. የአሮን ቤት ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

11. እናንተ እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 115