ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 108:1-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. አምላክ ሆይ፤ ልቤ ጽኑ ነው፤እዘምራለሁ፤ በፍጹም ነፍሴም እዘምራለሁ።

2. በገናም መሰንቆም ተነሡ፤እኔም ማልጄ እነሣለሁ።

3. እግዚአብሔር ሆይ፤ በሕዝብ መካከል አመሰግንሃለሁ፤በሕዝቦችም መካከል እዘምርልሃለሁ።

4. ምሕረትህ ከሰማያት በላይ ታላቅ ናትና፤ታማኝነትህም እስከ ጠፈር ትደርሳለች።

5. አምላክ ሆይ፤ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ በል፤ክብርህም በምድር ሁሉ ላይ ትንሰራፋ።

6. ወዳጆችህ ይድኑ ዘንድ፣በቀኝ እጅህ ታደግ፤ መልስልኝም።

7. እግዚአብሔር ከመቅደሱ እንዲህ አለ፤ደስ እያለኝ ሴኬምን እሸነሽናለሁ፤“የሱኮትንም ሸለቆ እለካለሁ።

8. ገለዓድ የእኔ ነው፤ ምናሴም የእኔ ነው፤ኤፍሬም የራስ ቍሬ ነው፤ይሁዳም በትረ መንግሥቴ።

9. ሞዓብ መታጠቢያ ገንዳዬ ነው፤በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እወረውራለሁ፤በፍልስጥኤም ላይ በድል አድራጊነት እፎክራለሁ።”

10. ወደ ተመሸገችው ከተማ ማን ይወስደኛል?ወደ ኤዶምያስስ ማን ያደርሰኛል?

11. እግዚአብሔር ሆይ፤ የጣልኸን አንተ አይደለህምን?አምላክ ሆይ፤ ከሰራዊታችንም ጋር አልወጣ አልህ!

12. አሁንም የሰው ማዳን ከንቱ ነውና፣በጠላታችን ላይ ድልን አቀዳጀን።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 108