ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 106:7-18 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. አባቶቻችን በግብፅ ሳሉ፣ታምራትህን አላስተዋሉም፤የምሕረትህን ብዛት አላሰቡም፤በባሕሩ አጠገብ፣ ገና ቀይ ባሕር አጠገብ ዐመፁብህ።

8. እርሱ ግን የኀይሉን ታላቅነት ለማሳወቅ፣ስለ ስሙ አዳናቸው።

9. ቀይ ባሕርን ገሠጸ፤ እርሱም ደረቀ፤በምድረ በዳ እንደሚታለፍ በጥልቅ ውሃ መካከል መራቸው።

10. ከባለጋራቸው እጅ አዳናቸው፤ከጠላትም እጅ ታደጋቸው።

11. ባላንጦቻቸውን ውሃ ዋጣቸው፤ከእነርሱም አንድ አልተረፈም።

12. ከዚህ በኋላ የተስፋ ቃሉን አመኑ፤በዝማሬም አመሰገኑት።

13. ነገር ግን ያደረገውን ወዲያውኑ ረሱ፤በምክሩም ለመሄድ አልታገሡም።

14. በምድረ በዳ እጅግ መመኘት አበዙ፤በበረሓም እግዚአብሔርን ተፈታተኑት።

15. እርሱም የለመኑትን ሰጣቸው፤ዳሩ ግን የሚያኰሰምን ሕመም ሰደደባቸው።

16. በሰፈር በሙሴ ላይ፣ ለእግዚአብሔር በተቀደሰውም በአሮን ላይ ቀኑ።

17. ምድር ተከፍታ ዳታንን ዋጠች፤የአቤሮንን ወገን ሰለቀጠች።

18. እሳት በጉባኤያቸው መካከል ነደደ፤ነበልባሉም ክፉዎችን ፈጅቶ አስወገደ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 106