ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 106:26-44 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

26. በምድረ በዳ ሊጥላቸው፣እጁን አንሥቶ ማለ፤

27. ዘራቸውንም በሕዝቦች መካከል ሊጥል፣ወደ ተለያየ ምድርም እንደሚበትናቸው ማለ።

28. ራሳቸውን ከብዔል ፌጎር ጋር አቈራኙ፤ለሙታን የተሠዋውን መሥዋዕት በሉ፤

29. በሥራቸውም እግዚአብሔርን አስቈጡት፤ቸነፈርም በላያቸው መጣ።

30. ፊንሐስም ተነሥቶ ጣልቃ ገባ፤ቸነፈሩም ተገታ፤

31. ይህም ከትውልድ እስከ ትውልድ፣ለዘላለም ጽድቅ ሆኖ ተቈጠረለት።

32. ደግሞም በመሪባ ውሃ አጠገብ እግዚአብሔርን አስቈጡት፤ሙሴም ከእነርሱ የተነሣ ተቸገረ፤

33. የእግዚአብሔርንም መንፈስ ስላስመረሩት፣ሙሴ የማይገባ ቃል ከአንደበቱ አወጣ።

34. እግዚአብሔር ባዘዛቸው መሠረት፣ሕዝቦችን ከማጥፋት ወደ ኋላ አሉ፤

35. እንዲያውም ከሕዝቦቹ ጋር ተደባለቁ፤ልማዳቸውንም ቀሠሙ፤

36. ጣዖቶቻቸውንም አመለኩ፤ይህም ወጥመድ ሆነባቸው።

37. ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውንለአጋንንት ሠዉ።

38. የወንዶችና የሴቶች ልጆቻቸውን ደም፣ለከነዓን ጣዖታት የሠዉአቸውን፣ንጹሕ ደም አፈሰሱ፤ምድሪቱም በደም ተበከለች።

39. በተግባራቸው ረከሱ፤በድርጊታቸውም አመንዝሮች ሆኑ።

40. ስለዚህ የእግዚአብሔር ቍጣ በሕዝቡ ላይ ነደደ፤ርስቱንም ተጸየፈ።

41. ለአሕዛብ አሳልፎ ሰጣቸው፤ጠላቶቻቸውም በላያቸው ሠለጠኑ።

42. ጠላቶቻቸው ጨቈኗቸው፤በሥልጣናቸውም ሥር አዋሏቸው።

43. እርሱ ብዙ ጊዜ ታደጋቸው፤እነርሱ ግን ዐመፃን የሙጥኝ አሉ፤በኀጢአታቸውም ተዋረዱ።

44. ሆኖም ጩኸታቸውን በሰማ ጊዜ፣ጭንቀታቸውን ተመለከተ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 106