ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 105:35-44 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

35. የምድሪቱንም ዕፀዋት ሁሉ በላ፤የመሬታቸውንም ፍሬ ሙጥጥ አደረገ፤

36. ደግሞም በአገራቸው ያለውን በኵር ሁሉ፣የኀይላቸውንም ሁሉ በኵራት መታ።

37. የእስራኤልንም ሕዝብ ብርና ወርቅ ጭኖ እንዲወጣ አደረገ፤ከነገዶቻቸውም አንድም አልተደናቀፈም።

38. እጅግ ፈርተዋቸው ነበርና፣ወጥተው ሲሄዱ ግብፅ ደስ አላት።

39. ደመናን እንደ መጋረጃ ዘረጋላቸው፤እሳትም በሌሊት አበራላቸው።

40. በለመኑትም ጊዜ፣ ድርጭት አመጣላቸው፤የሰማይንም እንጀራ አጠገባቸው።

41. ዐለቱን ሰነጠቀ፤ ውሃም ተንዶለደለ፤እንደ ወንዝም በበረሓ ፈሰሰ።

42. ለባሪያው ለአብርሃም የሰጠውን፣ቅዱስ የተስፋ ቃሉን አስቦአልና።

43. ሕዝቡን በደስታ፣ምርጦቹንም በእልልታ አወጣቸው።

44. የሌሎችን ሕዝቦች ምድር ሰጣቸው፤የእነዚህንም የድካም ፍሬ ወረሱ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 105