ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 104:30-35 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

30. መንፈስህን ስትልክ፣እነርሱ ይፈጠራሉ፤የምድርንም ገጽ ታድሳለህ።

31. የእግዚአብሔር ክብር ለዘላለም ጸንቶ ይኑር፤ እግዚአብሔር በሥራው ደስ ይበለው፤

32. እርሱ ምድርን ሲመለከት፣ ትንቀጠቀጣለች፤ተራሮችም እርሱ ሲዳስሳቸው ይጤሳሉ።

33. በሕይወት ሳለሁ ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ፤ቆሜ እስከ ሄድሁ ድረስም አምላኬን እወድሳለሁ።

34. እኔ በእግዚአብሔር ደስ እንደሚለኝ፣የልቤ ሐሳብ እርሱን ደስ ያሰኘው።

35. ኀጥአን ከምድር ገጽ ይጥፉ፤ዐመፀኞች ከእንግዲህ አይገኙ።ነፍሴ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኪ፤ሃሌ ሉያ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 104