ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 10:5-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. መንገዱ ዘወትር የተሳካ ነው፤ዕቡይ፣ ከሕግህም የራቀ ነው።በመሆኑም በጠላቶቹ ላይ ያፌዛል።

6. በልቡም፣ “ከስፍራዬ የሚነቀንቀኝ የለም፤ከትውልድ እስከ ትውልድም መከራ አያገኘኝም” ይላል።

7. አፉ መርገምን፣ ቅጥፈትንና ግፍን የተሞላ ነው፤ሽንገላና ክፋት ከምላሱ ሥር ይገኛሉ።

8. በየመንደሩ ሥርቻ ያደፍጣል፤ንጹሐንን በሰዋራ ስፍራ ይገድላል።ዐይኖቹንም በምስኪኖች ላይ ያነጣጥራል።

9. በደኑ ውስጥ እንዳለ አንበሳ በስውር ያደባል፤ረዳት የሌለውን ለመያዝ ያሸምቃል፤ድኻውንም አፈፍ አድርጎ በወጥመዱ ይጐትታል።

10. ምስኪኑም ይደቃል፤ ዐንገቱን ይደፋል፤ያልታደለውም በክንዱ ሥር ይወድቃል።

11. በልቡም፣ “እግዚአብሔር ረስቶአል፤ፊቱን ሸፍኖአል፤ ፈጽሞም አያይም”ይላል።

12. እግዚአብሔር ሆይ ተነሥ፤ አምላክ ሆይ፤ ክንድህን አንሣ፤ረዳት የሌላቸውንም አትርሳ።

13. ክፉ ሰው በእግዚአብሔር ላይ ለምን ክፉ ይናገራል?በልቡስ፣ “ስለ ሥራዬ አይጠይቀኝም”ለምን ይላል?

14. አንተ ግን መከራንና ሐዘንን ታያለህ፤በእጅህም ዋጋ ለመክፈል ትመለከታለህ፤ምስኪኑም ራሱን በአንተ ላይ ይጥላል፤ለድኻ ዐደግም ረዳቱ አንተ ነህ።

15. የክፉውንና የበደለኛውን ክንድ ስበር፤የእጁንም ስጠው፤ምንም እስከማይገኝ ድረስ።

16. እግዚአብሔር ከዘላለም እስከ ዘላለም ንጉሥ ነው፤ሕዝቦችም ከምድሩ ይጠፋሉ።

17. እግዚአብሔር ሆይ፤ የተገፉትን ምኞት ትሰማለህ፤ልባቸውን ታበረታለህ፤ ጆሮህንም ወደ እነርሱ ጣል ታደርጋለህ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 10