ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መክብብ 4:9-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. ለሥራቸው መልካም ውጤት ስለሚያገኙ፣ከአንድ፣ ሁለት መሆን ይሻላል፤

10. አንዱ ቢወድቅ፣ባልንጀራው ደግፎ ያነሣዋል።ቢወድቅ የሚያነሣው ረዳት የሌለው ግን፣እንዴት አሳዛኝ ነው!

11. ደግሞም ሁለቱ አብረው ቢተኙ ይሞቃቸዋል፤ነገር ግን አንዱ ብቻውን እንዴት ሊሞቀው ይችላል?

12. አንድ ሰው ብቸኛውን ቢያጠቃውም፣ሁለት ከሆኑ ይመክቱታል፤በሦስት የተገመደ ገመድም ቶሎ አይበጠስም።

13. ምክርን መቀበል ከማያውቅ ሞኝና ሽማግሌ ንጉሥ ይልቅ ጠቢብ የሆነ ድኻ ወጣት ይሻላል።

14. ወጣቱ ከእስር ቤት ወደ ንጉሥነት የመጣ ወይም በግዛቱ ውስጥ በድኽነት የተወለደ ሊሆን ይችላል።

15. ከፀሓይ በታች የሚኖሩና የሚመላለሱ ሁሉ፣ ንጉሡን የሚተካውን ወጣት ተከትለውት አየሁ።

16. በፊቱ የነበረው ሕዝብ ሁሉ ቊጥር ስፍር አልነበረውም፤ ከእርሱ በኋላ የመጡት ግን በተተኪው አልተደሰቱም። ይህም ደግሞ ከንቱ፣ ነፋስንም እንደ መከተል ነው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መክብብ 4