ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መክብብ 12:8-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. ሰባኪው “ከንቱ ከንቱሁሉም ነገር ከንቱ ነው!” ይላል።

9. ሰባኪው ጥበበኛ ብቻ አልነበረም፤ ነገር ግን ለሕዝቡ ዕውቀትንም ያስተምር ነበር። እርሱም በጥልቅ አሰበ፤ ተመራመረም፤ ብዙ ምሳሌዎችንም በሥርዐት አዘጋጀ።

10. ሰባኪው ትክክለኛውን ቃል ለማግኘት ተመራመረ፤ የጻፈውም ቅንና እውነት ነበረ።

11. የጠቢባን ቃላት እንደ ሹል የከብት መንጃ ናቸው፤ የተሰበሰቡ አባባሎቹም እጅግ ተቀብቅበው እንደ ገቡ ችንካሮች ሲሆኑ፣ ከአንድ እረኛ የተሰጡ ናቸው።

12. ልጄ ሆይ፤ ከዚህ ሁሉ በላይ በማንኛውም ነገር ተጠንቀቅ፤ አንዳችም አትጨምር።ብዙ መጻሕፍትን መጻፍ ማብቂያ የለውም፤ ብዙ ማጥናትም ሰውነትን ያደክማል።

13. እነሆ፤ ሁሉ ነገር ከተሰማ ዘንድ፣የነገሩ ሁሉ ድምዳሜ ይህ ነው፤እግዚአብሔርን ፍራ፤ ትእዛዛቱንም ጠብቅ፤ይህ የሰው ሁለንተናዊ ተግባሩ ነውና።

14. መልካምም ይሁን ክፉ፣ስውር የሆነውን ነገር ሁሉ አንድ ሳይቀር፣ማንኛውንም ሥራ እግዚአብሔር ወደ ፍርድ ያመጣዋልና።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መክብብ 12