ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መክብብ 10:1-14 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. የሞቱ ዝንቦች ሽቶን እንደሚያገሙ፣ትንሽ ሞኝነትም ጥበብንና ክብርን ያቀላል።

2. የጠቢብ ልብ ወደ ቀኝ፣የሞኝ ልብ ግን ወደ ግራ ያዘነብላል።

3. ሞኝ በጐዳና ሲሄድ ማስተዋል ይጐድለዋል፤ጅል መሆኑንም ለማንም ይገልጻል።

4. የገዥ ቊጣ በተነሣብህ ጊዜ፣ስፍራህን አትልቀቅ፤ትዕግሥት ታላቁን ጥፋት ጸጥ ያደርጋልና።

5. ከፀሓይ በታች ያየሁት ክፉ ነገር አለ፤ይህም ከገዥ የሚወጣ ስሕተት ነው፤

6. ሞኞች በብዙ የክብር ስፍራዎች ሲቀመጡ፣ሀብታሞች ግን በዝቅተኛ ስፍራ ሆነዋል።

7. መሳፍንት እንደ ባሮች በእግራቸው ሲሄዱ፣ባሮች ፈረስ ላይ ተቀምጠው አይቻለሁ።

8. ጒድጓድን የሚምስ ራሱ ይገባበታል፤ቅጥርንም የሚያፈርስ እባብ ይነድፈዋል።

9. ድንጋይ የሚፈነቅል ይጐዳበታል፤ግንድንም የሚፈልጥ አደጋ ላይ መውደቁ አይቀርም።

10. መጥረቢያ ቢደንዝ፣ጫፉም ባይሳል፣ብዙ ጒልበት ይጨርሳል፤ብልኀት ግን ለውጤት ያበቃል።

11. እባብ በድግምት ከመፍዘዙ በፊት ቢነድፍ፣ለደጋሚው ምንም አይጠቅመውም።

12. ከጠቢብ አፍ የሚወጣ ቃል ባለ ሞገስ ነው፤ሞኝ ግን በገዛ ከንፈሩ ይጠፋል፤

13. ቃሉ በመጀመሪያ ሞኝነት ነው፤በመጨረሻም ደግሞ ክፉ እብደት ነው፤

14. ሞኙም ቃልን ያበዛል።የሚመጣውን የሚያውቅ የለም፤ከእርሱ በኋላ የሚሆነውንስ ማን ሊነግረው ይችላል?

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መክብብ 10