ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሕዝቅኤል 29:1-4 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. በዐሥረኛው ዓመት፣ በዐሥረኛው ወር፣ በዐሥራ ሁለተኛው ቀን የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤

2. “የሰው ልጅ ሆይ፤ ፊትህን ወደ ግብፅ ንጉሥ ወደ ፈርዖን አዙር፤ በእርሱና በግብፅ ሁሉ ላይ ትንቢት ተናገር፤

3. እንዲህም ብለህ ተናገረው፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል።“ ‘በወንዞችህ መካከል የምትተኛ አንተ ታላቅ አውሬ፣የግብፅ ንጉሥ ፈርዖን፤ በአንተ ላይ ተነሥቻለሁ።“የዐባይ ወንዝ የእኔ ነው፤ለራሴም ሠርቼዋለሁ” ትላለህ።

4. ነገር ግን በመንጋጋህ መንጠቆ አስገባለሁ፤የወንዞችህን ዓሦች ከቅርፊትህ ጋር አጣብቃለሁ፤ቅርፊትህ ላይ ከተጣበቁት ዓሦች ሁሉ ጋር፣ከወንዞችህ ጐትቼ አወጣሃለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሕዝቅኤል 29