ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሕዝቅኤል 28:20-26 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

20. የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤

21. “የሰው ልጅ ሆይ፤ ፊትህን ወደ ሲዶና አዙር፤ ትንቢትም ተናገርባት፤

22. እንዲህም በል፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ ‘ሲዶን ሆይ፤ በአንቺ ላይ ተነሥቻለሁ፤በውስጥሽ እከብራለሁ፤ቅጣትን ሳመጣባት፣ቅድስናዬንም በውስጧ ስገልጥ፣እኔ እግዚአብሔር እንደሆንሁ ያውቃሉ።

23. በእርሷ ላይ መቅሠፍት አመጣለሁ፤በመንገዶቿ ላይ ደም እንዲፈስ አደርጋለሁ፤ከየአቅጣጫው በሚመጣ ሰይፍ፣የታረዱት በውስጧ ይወድቃሉ፤ከዚያም እኔ እግዚአብሔር እንደሆንሁ ያውቃሉ።

24. “ ‘ከእንግዲህ ወዲያ የእስራኤል ሕዝብ የሚያሠቃይ አሜከላና የሚወጋ እሾኽ የሆኑ ጎረቤቶች አይኖሯቸውም፤ ከዚያም እኔ ጌታ እግዚአብሔር እንደሆንሁ ያውቃሉ።

25. “ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ የእስራኤልን ሕዝብ ከተበተኑባቸው አገሮች መካከል በምሰበስብበት ጊዜ፣ አሕዛብ እያዩ ቅድስናዬን በመካከላቸው እገልጣለሁ፤ ከዚያም በገዛ ምድራቸው ይኖራሉ፤ ይህም ለባሪያዬ ለያዕቆብ የሰጠሁት ነው።

26. በዚያም በሰላም ይኖራሉ፤ ቤቶች ይሠራሉ፤ የወይን ተክል ቦታም ያበጃሉ። ያጣጣሏቸው ጎረቤቶቻቸውን ሁሉ በምቀጣበት ጊዜ እነርሱ በሰላም ይኖራሉ፤ ከዚያም እኔ እግዚአብሔር አምላካቸው እንደሆንሁ ያውቃሉ።’ ”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሕዝቅኤል 28