ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሕዝቅኤል 28:12-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. “የሰው ልጅ ሆይ፤ ስለ ጢሮስ ንጉሥ ሙሾ አውርድ፤ እንዲህም በለው፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ ‘ጥበብን የተሞላህ፣ ፍጹም ውበትን የተላበስህ፣የፍጹምነት ምሳሌ ነበርህ።

13. በእግዚአብሔር የአትክልት ቦታ፣በዔድን ነበርህ፤እያንዳንዱ የከበረ ድንጋይ አስጊጦህ ነበር፤ሰርድዮን፣ ቶጳዝዮን፣ አልማዝ፣መረግድ፣ ኢያሰጲድ፣ ሰንፔር፣በሉር፣ ቢረሌና የከበረ ዕንቍ።ልብስህም የሚያብረቀርቅ ዕንቍ ወርቅ ነበር፤የተዘጋጁትም አንተ በተፈጠርህበት ዕለት ነበር።

14. ጠባቂ ኪሩብ ሆነህ ተቀብተህ ነበር፤ለዚሁም ሾምሁህ፤በእግዚአብሔር ቅዱስ ተራራ ላይ ነበርህ፤በእሳት ድንጋዮች መካከል ተመላለስህ።

15. ከተፈጠርህበት ቀን ጀምሮ፣ክፋት እስከ ተገኘብህ ድረስ፣በመንገድህ ነቀፌታ አልነበረብህም።

16. ንግድህ ስለ ደረጀ፣በዐመፅ ተሞላህ፣ኀጢአትም ሠራህ፤ስለዚህ ከእግዚአብሔር ተራራ በውርደት አሳደድሁህ፤ጠባቂ ኪሩብ ሆይ፤ ከእሳት ድንጋዮችመካከል አስወጣሁህ።

17. በውበትህ ምክንያት፣ልብህ ታበየ፤ከክብርህ ታላቅነት የተነሣም፣ጥበብህን አረከስህ።ስለዚህ ወደ ምድር ወረወርሁህ፤ለነገሥታት ትዕይንት አደረግሁህ።

18. በኀጢአትህና በተጭበረበረው ንግድህ ብዛት፣መቅደስህን አረከስህ።ስለዚህ እሳት ከአንተ እንዲወጣ አደረግሁ፤እርሱም በላህ፤በሚመለከቱህ ሁሉ ፊት፣በምድር ላይ ዐመድ አደረግሁህ።

19. የሚያውቁህን አሕዛብ ሁሉ፣ሁኔታህ አስደንግጦአቸዋል፤መጨረሻህ የሚያሳዝን ሆነ፤ከእንግዲህ ሕልውና የለህም።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሕዝቅኤል 28