ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14
  15. 15
  16. 16
  17. 17
  18. 18
  19. 19
  20. 20
  21. 21
  22. 22
  23. 23
  24. 24
  25. 25
  26. 26
  27. 27
  28. 28
  29. 29
  30. 30
  31. 31
  32. 32
  33. 33
  34. 34
  35. 35
  36. 36
  37. 37
  38. 38
  39. 39
  40. 40
  41. 41
  42. 42
  43. 43
  44. 44
  45. 45
  46. 46
  47. 47
  48. 48

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሕዝቅኤል 27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

ለጢሮስ የወጣ ሙሾ

1. የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፤

2. “የሰው ልጅ ሆይ፤ ስለ ጢሮስ ሙሾ አውርድ፤

3. በባሕር መግቢያ ላይ ለምትገኘውና በብዙ ጠረፎች ከሚኖሩ ሕዝቦች ጋር ለምትነግደው ለጢሮስ እንዲህ በላት፤ ‘ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“ ‘ጢሮስ ሆይ!፤“ፍጹም ውብ ነኝ” ብለሻል፤

4. ዳርቻሽ በባሕር መካከል ነው፤ሠሪዎችሽም ፍጹም ውብ አድርገውሻል።

5. ሳንቃዎችሽን ሁሉ፣ከሳኔር በመጣ ጥድ ሠሩ፤ደቀልንም ይሠሩልሽ ዘንድ፤ከሊባኖስ ዝግባ አመጡ።

6. ከባሳን በመጣ ወርካ፣መቅዘፊያሽን ሠሩ፤ከቆጵሮስ ጠረፍ በመጣ ዝግባ፣በዝኆን ጥርስ ለብጠው ወለልሽን ሠሩ።

7. የመርከቦችሽ ሸራ ጥልፍ ሥራ ያለበት የግብፅ በፍታ ነበረ፤ይህም እንደ ዐርማ አገለገለሽ።መጋረጃዎችሽ ከኤሊሳ ጠረፍ የመጡ፣ባለ ሰማያዊና ሐምራዊ ቀለም ነበሩ።

8. ቀዛፊዎችሽ ከሲዶናና ከአራድ የመጡ ነበሩ፤ጢሮስ ሆይ፤ የራስሽ ጠቢባን የመርከቦችሽ መሪዎች ነበሩ።

9. ልምድ ያካበቱ የጌባል ባለ ሙያዎች፣መርከብሽን ለመገጣጠም በመካከልሽ ነበሩ፤የባሕር መርከቦችና መርከበኞቻቸው ሁሉ፣ከአንቺ ጋር ሊገበያዩ ይመጡ ነበር።

10. “ ‘የፋርስ፣ የሉድና የፉጥ ሰዎች፣ወታደር ሆነው በሰራዊትሽ ውስጥአገለገሉ፤ሞገስም ይሆኑሽ ዘንድ፣ጋሻቸውንና የራስ ቍራቸውን በግድግዳሽ ላይ ሰቀሉ።

11. የአራድና የሔሌክ ሰዎች፣ቅጥርሽን በየአቅጣጫው ጠበቁ፤የገማድ ሰዎችም፣ በምሽግሽ ውስጥ ነበሩ።ጋሻቸውንም በቅጥርሽ ዙሪያ ሰቀሉ፤ውበትሽንም ፍጹም አደረጉ።

12. “ ‘ከሀብትሽ ብዛት የተነሣ፣ ተርሴስ ከአንቺ ጋር የንግድ ልውውጥ ታደርግ ነበር፤ ብርና ብረት፣ ቈርቈሮና እርሳስ አምጥታ ሸቀጥሽን ትለውጥ ነበር።

13. “ ‘ያዋን፣ ቶቤልና ሞሳሕ ከአንቺ ጋር ይነግዱ ነበር፤ ባሪያዎችንና የናስ ዕቃዎችን በሸቀጥሽ ይለውጡ ነበር።

14. “ ‘የቤት ቴርጋማ ሰዎችም መጋዣዎችን፣ የጦር ፈረሶችንና በቅሎዎችን በሸቀጥሽ ለወጡ።

15. “ ‘የድዳን ሰዎች ከአንቺ ጋር ተገበያዩ፤ብዙ የጠረፍ አገሮችም የንግድ ደንበኞችሽ ነበሩ፤ በዝኆን ጥርስና በዞጲ ሸቀጥሽን ይገዙ ነበር።

16. “ ‘ምርትሽ ብዙ እንደ መሆኑ፣ ሶርያ ከአንቺ ጋር ትገበያይ ነበር፤ ሸቀጥሽንም በበሉር፣ በሐምራዊ ጨርቅ፣ በወርቀ ዘቦ፣ በጥሩ በፍታ፣ በዛጐልና በቀይ ዕንቍ ይለውጡ ነበር።

17. “ ‘ይሁዳና እስራኤል እንኳ ከአንቺ ጋር ተገበያይተዋል፤ የሚኒትን ስንዴ፣ ጣፋጭ ቂጣ፣ ማር፣ ዘይትና በለሳን በማምጣት በሸቀጥሽ ይለውጡ ነበር።

18. “ ‘ከሀብት ከንብረትሽ ብዛት የተነሣ፣ ደማስቆ የኬልቦንን የወይን ጠጅና፣ የዛሐርን የበግ ጠጒር በማቅረብ ከአንቺ ጋር ተገበያ ይታለች።

19. “ ‘ዌንዳንና ያዋን ከኦሴል መጥተው ከአንቺ ጋር የንግድ ልውውጥ ያደርጉ ነበር፤ ቀልጦ የተሠራ ብረትን፣ ብርጒድንና ቀረፋን በሸቀጥሽ ይለውጡ ነበር።

20. “ ‘ድዳን ግላስ በማቅረብ ከአንቺ ጋር ትነግድ ነበር።

21. “ ‘የዐረብና የቄዳር መሳፍንት ሁሉ ደምበኞችሽ ነበሩ፤ ጠቦትና አውራ በግ፣ ፍየልም አምጥተው ከአንቺ ጋር ይገበያዩ ነበር።

22. “ ‘የሳባና የራዕማ ነጋዴዎች ከአንቺ ጋር ይገበያዩ ነበር፤ ምርጥ የሆነውን የሽቱ ቅመም ዐይነት ሁሉ፣ የከበረ ድንጋይና ወርቅ በማቅረብ በሸቀጥሽ ይለውጡ ነበር።

23. “ ‘ካራን፣ ካኔ፣ ዔደን፣ የሳባ ነጋዴዎች፣ አሦርና ኪልማድ ከአንቺ ጋር የንግድ ልውውጥ ያደርጉ ነበር።

24. እነዚህም በገበያሽ ውስጥ ያማረ ልብስ፣ ሰማያዊ ካባ፣ ወርቀ ዘቦ እንዲሁም በኅብረ ቀለም ያሸበረቀና በጥብቅ የተታታ ስጋጃ በማቅረብ ከአንቺ ጋር ይነግዱ ነበር።

25. “ ‘የተርሴስ መርከቦች፣ሸቀጥሽን አጓጓዙልሽ፤በባሕር መካከልም፣በከባድ ጭነት ተሞልተሽ ነበር።

26. ቀዛፊዎችሽ፣ወደ ጥልቁ ባሕር ይወስዱሻል፤የምሥራቁ ነፋስ ግን፣በባሕሩ መካከል ይሰባብርሻል።

27. የመርከብ አደጋ በሚደርስበሽ ቀን፣ሀብትሽ፣ ሸቀጥሽና የንግድ ዕቃሽ፣መርከብ ነጂዎችሽ፣ መርከበኞችሽና መርከብ ሠሪዎችሽ፣ነጋዴዎችሽና ወታደሮችሽ ሁሉ፣በመርከብ ላይ ያሉትም ሁሉ፣ወደ ባሕሩ ወለል ይዘቅጣሉ።

28. መርከበኞችሽ ሲጮኹ፣የባሕሩ ጠረፍ ይናወጣል።

29. ቀዛፊዎች ሁሉ፣መርከባቸውን ጥለው ይሄዳሉ፤መርከብ ነጂዎችና መርከበኞችም ሁሉ፣ወርደው ባሕሩ ዳር ይቆማሉ፤

30. ድምፃቸውን ከፍ አድርገው፣በምሬት ያለቅሱልሻል፤በራሳቸውም ላይ ዐቧራ ነስንሰው፣በዐመድ ላይ ይንከባለላሉ።

31. ስለ አንቺ ጠጒራቸውን ይላጫሉ፤ማቅም ይለብሳሉ፤በነፍስ ምሬት፣በመራራም ሐዘን ያለቅሱልሻል።

32. ስለ አንቺ በዋይታ ያለቅሳሉ፤እንዲህም እያሉ ሙሾ ያወርዳሉ፤“ባሕር ውጦት የቀረ፣እንደ ጢሮስ ማን አለ?”

33. ሸቀጥሽ ከባሕር በወጣ ጊዜ፤ብዙ ሕዝቦችን ታጠግቢ ነበር፣በታላቅ ሀብትሽና ሸቀጥሽ፣የምድርን ነገሥታት ታበለጽጊ ነበር።

34. አሁን ግን በጥልቅ ውሃ ውስጥ፣በባሕር ተንኰታኵተሻል፤ጭነትሽና ተሳፋሪዎችሽ ሁሉ፣ከአንቺ ጋር ሰጥመዋል።

35. በጠረፍ አገር የሚኖሩ ሁሉ፣በአንቺ ሁኔታ ተደናገጡ፤ንጉሦቻቸው በፍርሀት ራዱ፤ፊታቸውም ተለዋወጠ።

36. በሌሎች ሕዝቦች መካከል ያሉ ነጋዴዎች ምንኛ አፏጩብሽ!መጨረሻሽ አስደንጋጭ ሆነ፤ለዘላለምም አትገኚም።’ ”