ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሕዝቅኤል 21:10-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. የተሳለው ሊገድል፣የተወለወለውም እንደ መብረቅ ሊብረቀረቅ ነው!“ ‘ታዲያ፣ እንዴት ደስ ሊለን ይችላል? ሰይፉ የልጄን በትረ መንግሥት እንደ ማንኛውም በትር ንቆአል።

11. “ ‘በእጁ እንዲያዝ፣ሰይፉ ሊወለወል ተሰጥቶአል፤ገዳዩ በእጁ እንዲጨብጠው፣ተስሎአል፤ ተወልውሎአል።

12. የሰው ልጅ ሆይ፤ ይህ በሕዝቤ ላይ፣በእስራኤልም መሳፍንት ሁሉ ላይ መጥቶአልና፤ጩኸት፣ ዋይታም አሰማ።እነርሱ ከሕዝቤ ጋር በአንድ ላይ፣ለሰይፍ ተጥለዋል፤ስለዚህ ደረትህን ምታ።

13. “ ‘ፈተና በእርግጥ ይመጣል፤ ሰይፉ የናቀው በትረ መንግሥት ዘላቂነት ባይኖረውስ? ይላል ጌታ እግዚአብሔር።’

14. “እንግዲህ፣ የሰው ልጅ ሆይ፤ ትንቢት ተናገር፤በእጅህም አጨብጭብ፤ሰይፉ ሁለት ጊዜ፣ሦስት ጊዜም ይምታ፤በእጅጉ የሚገድል፣ለግድያ የሚሆን፣በየአቅጣጫውም የሚከባቸው ሰይፍ ነው።

15. ልብ ሁሉ ይቀልጥ ዘንድ፣የሚወድቁትም እንዲበዙ፣በበሮቻቸው ሁሉ፣የግድያውን ሰይፍ አኑሬአለሁ።ወዮ! እንዲያብረቀርቅ ተወልውሎአል፤ለመግደልም ተመዞአል።

16. ሰይፍ ሆይ፤ በስለትህ አቅጣጫ ሁሉ፣ወደ ቀኝም፣ወደ ግራም ቍረጥ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሕዝቅኤል 21