ምዕራፎች

  1. 1
  2. 2
  3. 3
  4. 4
  5. 5
  6. 6
  7. 7
  8. 8
  9. 9
  10. 10
  11. 11
  12. 12
  13. 13
  14. 14

ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሆሴዕ 7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. እስራኤልን በምፈውስበት ጊዜ፣የኤፍሬም ኀጢአት፣የሰማርያም ክፋት ይገለጣል።እነርሱ ያጭበረብራሉ፤ሌቦች ቤቶችን ሰብረው ይገባሉ፤ወንበዴዎችም በየመንገድ ይዘርፋሉ።

2. ነገር ግን ክፉ ድርጊታቸውን ሁሉ እንደማስታውስ፣እነርሱ አይገነዘቡም፤ኀጢአታቸው ከቦአቸዋል፤ሁልጊዜም በፊቴ ናቸው።

3. “ንጉሡን በክፋታቸው፣አለቆችንም በሐሰታቸው ያስደስታሉ።

4. ሊጡ ቦክቶ ኩፍ እንደሚል፣ዳቦ ጋጋሪው እሳት መቈስቈስ እስከማያስፈልገው ድረስ፣እንደሚነድ ምድጃ፣ሁሉም አመንዝራ ናቸው።

5. በንጉሣችን የበዓል ቀን፣አለቆች በወይን ጠጅ ስካር ጋሉ፤እርሱም ከፌዘኞች ጋር ተባበረ።

6. ልባቸው እንደ ምድጃ የጋለ ነው፤በተንኰል ይቀርቡታል፤ቍጣቸው ሌሊቱን ሙሉ ይጤሳል፤እንደሚነድም እሳት በማለዳ ይንበለበላል።

7. ሁሉም እንደ ምድጃ የጋሉ ናቸው፤ገዦቻቸውን ፈጁ፤ንጉሦቻቸው ሁሉ ወደቁ፤ከእነርሱም ወደ እኔ የቀረበ ማንም የለም።

8. “ኤፍሬም ከአሕዛብ ጋር ተደባለቀ፤ኤፍሬም ያልተገላበጠ ቂጣ ነው።

9. እንግዶች ጒልበቱን በዘበዙ፤እርሱ ግን አላስተዋለም።ጠጒሩም ሽበት አወጣ፤እርሱ ግን ልብ አላለም።

10. የእስራኤል ትዕቢት በራሱ ላይ መሰከረበት፤ይህ ሁሉ ሆኖ ግን፣ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር አልተመለሰም፤እርሱንም አልፈለገም።

11. ኤፍሬም በቀላሉ እንደምትታለል፣አእምሮም እንደሌላት ርግብ ነው፤አንድ ጊዜ ወደ ግብፅ ይጣራል፤ሌላ ጊዜ ደግሞ ወደ አሦር ይዞራል።

12. ሲበሩ፣ መረቤን በላያቸው እዘረጋለሁ፤እንደ ሰማይ ወፎችም ጐትቼአወርዳቸዋለሁ፤ስለ ክፉ ሥራቸውም በጒባኤ መካከል እቀጣቸዋለሁ።

13. ወዮ ለእነርሱ፤ከእኔ ርቀው ሄደዋልና!ጥፋት ይምጣባቸው!በእኔ ላይ ዐምፀዋልና።ልታደጋቸው ፈለግሁ፤እነርሱ ግን በእኔ ላይ ሐሰት ይናገራሉ።

14. ከልባቸው ወደ እኔ አይጮኹም፤ነገር ግን በዐልጋቸው ላይ ሆነው ያለቅሳሉ።ስለ እህልና ስለ አዲስ የወይን ጠጅይሰበሰባሉ፤ነገር ግን ከእኔ ዘወር ብለዋል።

15. እኔ አሠለጠንኋቸው፤ አጠነከርኋቸውም፤እነርሱ ግን አደሙብኝ።

16. ወደ ከንቱ ነገር ተመለሱ፤ዒላማውን እንደሳተ ቀስት ናቸው፤መሪዎቻቸው ስለ ክፉ ቃላቸው፣በሰይፍ ይወድቃሉ፤በዚህም ምክንያት በግብፅ ምድር፣መዘባበቻ ይሆናሉ።