ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሆሴዕ 2:1-6 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

1. “ወንድሞቻችሁን ‘ሕዝቤ’፣ እኅቶቻችሁንም ‘ተወዳጆቼ’ ብላችሁ ጥሯቸው።

2. “እናታችሁን ምከሯት፤ ምከሯት፤እርሷ ሚስቴ አይደለችም፤እኔም ባሏ አይደለሁምና።ከፊቷ የዘማዊነት አስተያየትን፣ከጡቶቿም መካከል ምንዝርናዋን ታስወግድ።

3. አለበለዚያ ገፍፌ ዕርቃኗን አስቀራታለሁ፤እንደ ተወለደችበትም ቀን አደርጋታለሁ፤እንደ ምድረ በዳ፣እንደ ደረቅም ምድር አደርጋታለሁ፤በውሃ ጥምም እገድላታለሁ።

4. ለልጆቿ አልራራላቸውም፤የምንዝርና ልጆች ናቸውና።

5. እናታቸው አመንዝራ ነች፤በውርደትም ፀንሳቸዋለች፤እርሷም፣ ‘እንጀራዬንና ውሃዬን ይሰጡኛል፤ሱፌንና የሐር ልብሴን፣ ዘይቴንና መጠጤን ይሰጡኛል፤ስለዚህ ውሽሞቼን ተከትዬ እሄዳለሁ’ አለች።

6. በዚህ ምክንያት መንገዷን በእሾህ እዘጋለሁ፤መውጫ መንገድ እንዳታገኝም ዙሪያዋን በግንብ አጥራለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሆሴዕ 2