ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሆሴዕ 10:2-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. ልባቸው አታላይ ነው፤ስለዚህም በደላቸውን ይሸከማሉ። እግዚአብሔር መሠዊያዎቻቸውን ያወድማል፤የጣዖት ማምለኪያ ዐምዶቻቸውን ያፈራርሳል።

3. እነርሱም፣ “እኛ ንጉሥ የለንም፤ እግዚአብሔርን አላከበርንምና፤ንጉሥ ቢኖረንስ፣ምን ሊያደርግልን ይችል ነበር?” ይላሉ።

4. ከንቱ ተስፋ ይሰጣሉ፤በሐሰት በመማል፣ቃል ኪዳን ያደርጋሉ፤ስለዚህም ፍርድ፣በዕርሻ ውስጥ እንደሚገኝ መርዛማ ዐረም ይበቅላል።

5. በሰማርያ የሚኖረው ሕዝብ፣በቤትአዌን ስላለው የጥጃ ጣዖት ይፈራል፤ሕዝቡም ያለቅስለታል፤በክብሩ እጅግ ደስ ያላቸው ሁሉ፣አመንዝራ ካህናትም እንደዚሁ ያለቅሱለታል፤በምርኮ ከእነርሱ ተወስዶአልና።

6. ለታላቁ ንጉሥ እንደ እጅ መንሻ፣ወደ አሦር ይወሰዳል፤ኤፍሬም ይዋረዳል፤እስራኤልም ስለ ጣዖቱ ያፍራል።

7. ሰማርያና ንጉሥዋ፣በውሃ ላይ እንዳለ ኩበት ተንሳፍፈው ይጠፋሉ።

8. የእስራኤል ኀጢአት የሆነው፣የአዌን ማምለኪያ ኰረብታ ይጠፋል፤እሾኽና አሜኬላ ይበቅልባቸዋል፤መሠዊያዎቻቸውንም ይወርሳል፤በዚያን ጊዜ ተራሮችን፣ “ሸፍኑን!”ኰረብታዎችንም፣ “ውደቁብን!” ይላሉ።

9. “እስራኤል ሆይ፤ ከጊብዓ ጊዜ ጀምሮ ኀጢአት ሠራችሁ፤በዚያም ጸናችሁ፤በጊብዓ የነበሩትን ክፉ አድራጊዎች፣ጦርነት አልጨረሳቸውምን?

10. በፈለግሁ ጊዜ እቀጣቸዋለሁ፤ስለ ድርብ ኀጢአታችሁም ይቀጧቸው ዘንድ፣በእነርሱ ላይ ይሰበሰባሉ፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሆሴዕ 10