ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

2 ሳሙኤል 23:22-33 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

22. የዮዳሄ ልጅ የበናያስ ጀግንነት እንደዚህ ያለ ነበረ፤ እርሱም እንደ ሦስቱ ኀያላን ሁሉ ዝናን ያተረፈ ሲሆን፣

23. ከሠላሳዎቹ ሁሉ በላይ የከበረ ሰው ነበረ፤ ነገር ግን ከሦስቱ እንደ አንዱ አልነበረም። ዳዊትም የክብር ዘበኞቹ አለቃ አድርጎ ሾመው።

24. ከሠላሳዎቹ መካከል የሚከተሉት ይገኙ ባቸዋል፤የኢዮአብ ወንድም አሣሄል፣የቤተ ልሔሙ ሰው የዱዲ ልጅ ኤልያናን፣

25. አሮዳዊው ሣማ፣አሮዳዊው ኤሊቃ፣

26. ፈሊጣዊው ሴሌስ፣የቴቁሐዊው የዒስካ ልጅ ዒራስ፣

27. ዓናቶታዊው አቢዔዜር፤ኩሳታዊው ምቡናይ፣

28. አሆሃዊው ጸልሞን፣ነጦፋዊው ማህራይ፣

29. የነጦፋዊው የበዓና ልጅ ሔሌብ፣ከብንያም ወገን የጊብዓ ሰው የሆነው የሪባይ ልጅ ኢታይ፣

30. ጲርዓቶናዊው በናያስ፣የገዓስ ሸለቆ ሰው ሂዳይ፣

31. ዓረባዊው አቢዓልቦን፣በርሑማዊው ዓዝሞት፣

32. ሸዓልቦናዊው ኤሊያሕባ፣የአሳን ልጆች፤ ዮናታን የተባለው፣

33. የአሮዳዊው የሣማ ልጅ፣የአሮዳዊው የሻራር ልጅ አሒአም፤

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 2 ሳሙኤል 23