ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

2 ሳሙኤል 22:37-46 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

37. እርምጃዬን አሰፋህ፤እግሮቼም አልተሰነካከሉም።

38. “ጠላቶቼን አሳደድሁ፤ አጠፋኋቸውም፤እስኪደመሰሱም ድረስ ወደ ኋላ አልተመለስሁም።

39. ፈጽሜ አጠፋኋቸው፤ ተመልሰውም መቆም አልቻሉም፤ከእግሬም ሥር ወድቀዋል።

40. ለጦርነት ኀይልን አስታጠቅኸኝ፣ተቃዋሚዎቼንም ከእግሬ ሥር አንበረከካቸው።

41. ጠላቶቼ ፊታቸውን አዙረው እንዲሸሹ አደረግሃቸው።ባላንጣዎቼንም ደመሰስኋቸው።

42. ለርዳታ ጮኹ፤ ያዳናቸው ግን አልነበረም፤ ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ እርሱ ግንአልመለሰላቸውም።

43. በምድር ላይ እንዳለ ትቢያ አድቅቄ ፈጨዃቸው፤በመንገድም ላይ እንዳለ ጭቃ ወቀጥኋቸው፤ ረገጥኋቸውም።

44. “በሕዝቤ ከተቃጣብኝ አደጋ አዳንኸኝ፤የመንግሥታትም ራስ አደረግኸኝ።የማላውቀው ሕዝብ ተገዛልኝ፤

45. ባዕዳን ሊለማመጡኝ መጡ፤እንደ ሰሙኝም ወዲያውኑ ይታዘዙኛል።

46. ባዕዳን ፈሩ፤ከምሽጋቸውም እየተንቀጠቀጡ ወጡ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ 2 ሳሙኤል 22